አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ ) በ35ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ የተሳተፉ የሀገራት መሪዎች ወደ ሀገራቸው እየተመለሱ ይገኛሉ።
በዚህ መሠረትም የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ማምሻውን ወደ ሀገራቸው አቅንተዋል።
በወቅቱም የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል፣ የፍትህ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞትዮስ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ እና ሌሎች የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች አሸኛኘት አድርገውላቸዋል።