አዲስ አበባ፣ የካቲት 4፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ወላይታ ዲቻ መከላከያን በማሸነፍ 3ኛ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል፡፡
በ12ኛው የቤት ኪንግ ፕሪምየር ሊግ በድሬዳዋ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ወላይታ ዲቻ መከላከያን 1 ለ 0 በማሸነፍ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል፡፡
አንተነህ ጉግሳ የወላይታ ዲቻን የማሸነፊያ ጎል በ7ኛው ደቂቃ ላይ አስቆትሯል፡፡
የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 12ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ቀጥለው ሲካሄዱ አርባ ምንጭ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ ምሽት 1 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ትላንት በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ ቡና አዲስ አበባ ከተማን 1 ለ 0 ሲያሸንፍ ባህርዳር ከተማ ሀዋሳ ከተማን 2 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው፡፡
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!