Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ከመጪው የዝናብ ወቅት አስቀድሞ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ዝግጅት እናድርግ – ጠ/ሚ ዐቢይ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 1 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከመጪው የዝናብ ወቅት አስቀድሞ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በመላ ሃገሪቱ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባ አስገነዘቡ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ክረምት ሳይገባ ለዘንድሮው የአረንጓዴዐሻራ መርሐ ግብር የዝናብ ውኃ ለማቆር እና የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል የሚደረገው ጥረት እጅግ ተስፋ ሰጪ መሆኑን አስታውቀዋል።

ከዚህ ጋር ተያይዞም ለአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ከመጪው የዝናብ ወቅት አስቀድሞ በቂ ዝግጅት ማድረግ ይገባል ብለዋል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version