Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በጤና ተቋማት ውስጥ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ ከአጋር ድርጅቶች ጋር እንሰራለን – ዶ/ር ሊያ ታደሰ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጤና ተቋማት ውስጥ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ ከአጋር ድርጅቶች ጋር እንሰራለን ሲሉ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ገለጹ።

ዶክተር ሊያ ይህንን ያሉት ዛሬ በጅማ ዞን ሰቃ ጮቆርሳ ወረዳ የተለያዩ የጤና ተቋማትን በጎበኙበት ወቅት ነው።

የሰቃ ጮቆርሳ ሆስፒታልና ሌሎች የጤና ተቋማትን ሲጎበኙም ፥ የአንቡላንስና የህክምና መሳሪያዎች እጥረት በጤና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ችግር እየፈጠረ መሆኑን ባለሙያዎችና የሃገር ሽማግሌዎች ለሚኒስትሯ ገልጸውላቸዋል።

ዶክተር ሊያ በዚህ ወቅት እንዳሉት ፥ ችግሮቹ በሌሎች የጤና ተቋማት ውስጥ መኖራቸውንና አጋር ድርጅቶችን በማሳተፍ ለመቅረፍ ይሰራል።

ሚኒስትሯ አክለውም የጅማ ዞን ነዋሪዎች፣ አመራሮችና ባለሙያዎች የጤና ተቋማትን ለማስፋፋትና ለማሻሻል በቅንጅት እየሰሩ ላሉት ስራ አድናቆታቸውን ገልፀዋል።

በሙክታር ጠሃ

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version