አዲስ አበባ፣ መጋቢት 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ ከክልሉ የፀጥታ ዓብይ ኮሚቴና ከጅግጅጋ ከተማ አስተዳደር አመራሮች ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም በረመዳን ጾም ወቅት የጅግጅጋ ከተማን ብሎም የክልሉን ሰላም ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡
ከዚህ ባለፈም ከረመዳን ጾም ጋር ተያይዞ የእሳት አደጋዎችን አስቀድሞ መከላከል እና የቁጥጥር ስራዎችን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መወያየታቸውን የክልሉ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ ዘግቧል፡፡
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

