Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀ የዓባይ ህብረ ዝማሬ እየተመረቀ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀ የዓባይ ህብረ ዝማሬ እየተመረቀ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው ያዘጋጀው ህብረ ዝማሬ ዋና ትኩረቱ የዓባይ ወንዝን በተመለከተ ከፍ ያለ ሃገራዊ ስሜት ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ተነግሯል።

ከህብረ ዝማሬው በተጨማሪ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ እና አለም ዓቀፍ የጥናት ማዕከል ማስጀመሪያ መርሃ ግብርም እየተካሄደ ይገኛል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣ የጎንደር ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር አስራት አጸደ ወይን እና ሌሎች እንግዶች ታድመዋል።

በለይኩን ዓለም

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version