Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በኢትዮጵያ እና ጣሊያን መካከል የ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ዩሮ የእርዳታ ስምምነት ተፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያና በጣሊያን መንግስታት መካከል የ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ዩሮ የእርዳታ ስምምነት ተፈርሟል፡፡
እርዳታው የምግብ አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ በምግብ ገበያና በምግብ ዝግጅት ወቅት የሚከሰተውን የምግብ ጥራትና ንጽህና መጓደልን በመከላከል የምግብ ደህንነትን ለማረጋገጥ ለታቀደው ፕሮጀክት የሚውል መሆኑ ታውቋል፡፡
Exit mobile version