አዲስ አበባ፣ ግንቦት 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በማዕድን ሚኒስቴር የሚገኘው የኢትዮጵያ የማዕድን ማሳያ (ጋለሪ) ተመርቆ ተከፍቷል።
የማዕድን ማሳያው በኢትዮጵያ በርካታ ማዕድናት መገኘታቸውን የሚጠቁም እና በየትኛው አከባቢ ምን አይነት ማዕድን እንዳለ መረጃ የሚሰጥ ሲሆን÷ ከዛሬ ጀምሮ ለእይታ ክፍት ይሆናል ተብሏል፡፡
የማዕድን ሚኒስትር ኢንጂነር ታከለ ኡማ ÷ ማሳያውን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ለባለሀብቶች፣ ለአምባሳደሮችና ለውጭ የማዕድን ካምፓኒ ተወካዮች ጋለሪውን አስጎብኝተዋል።
ለኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ያለው ሀሳብ ከተቋማዊ ሪፎርም ጀምሮ በተግባር እየተገለጠ መሆኑን ጠቅሰው÷ የምንሰራቸው የሪፎርም ስራዎች የኢትዮጵያን የማዕድን ዘርፍ በሚገባው ቦታ ላይ ለማስቀመጥ ነው ብለዋል፡፡
ማሳያውን በይፋ የከፈቱት የማዕድን ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሚሊየን ማቲዎስ ÷ ማሳያው ኢትዮጵያ በርካታ ማዕድናት እንዳሏት መረጃ የሚሰጥ ነው ብለዋል።
በታሪኩ ለገሰ
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

