አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲስ አበባ የሚገኙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች ፣የዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ፡፡
አምባሳደሮች ፣የዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች የአብርሆት ቤተ መፃህፍትን ፣ አንድነት ፓርክን ፣በጠቅላይ ሚኒስቴር ፅ/ቤት እየተከናወነ ያለውን ሞዴል የገፅ ምድር ልማት ናሙና አግድም እርሻ እና ጓሮ አትክልት ጎብኝተዋል፡፡
እንዲሁም የማዕድን ሚኒስቴርን የማዕድን ማሳያ ማዕከልን ጨምሮ ሌሎች ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው መጎብኘታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

