Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በኩዌት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው የሚያደርጉትን ድጋፍ ማጠናከር በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 6 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኩዌት የኢትዮጵያ አምባሳደር ሐሰን ታጁ በሀገሪቷ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለሃገራቸው የሚያደርጉትን ድጋፍ ማጠናከር በሚቻልበት አግባብ ላይ ተወያዩ፡፡

አምባሳደሩ በቀጣይ ማኅበረሰቡን በሚያስፈልገው ሁሉ ለመደገፍ ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።

በኩዌት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው የሚያደርጉትን ድጋፍ እንዲቀጥሉና መብታቸውን ለማስከበር ከኤምባሲው ጋር በቅርበት እንዲሠሩም ጠይቀዋል።

ከውይይቱ በኋላ በኩዌት ሆስፒታል በመገኘት የሚገኙ ታካሚ ኢትዮጵያውንን መጎብኘታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version