Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

አምባሳደሩ መንግስት በሠላም ማሥፈን እና ልማት ላይ የተገበራቸውን ሥራዎች ለብሪታኒያ የፓርላማ አባላት አስረዱ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈሪ መለሰ መንግስት በሀገሪቱ ዘላቂ ሠላም ለማስፈን የወሰዳቸውን እርምጃዎች በኢትዮጵያና በጂቡቲ ጉዳይ ላይ ለተቋቋመው የብሪታኒያ የፓርላማ አባላት አስረድተዋል፡፡

አምባሳደር ተፈሪ ፥ ህወሓት ለሦስተኛ ዙር ወታደራዊ ጥቃት እየተዘጋጀ መሆኑንም ነው ያስረዱት፡፡

ህወሓት ጥቃቱን ለመፈጸም የተዘጋጀው ታዳጊ ሕጻናትን በመመልመል ጭምር መሆኑ ደግሞ ጉዳዩን ይበልጥ አሳሳቢ እንደሚያደርገውም ነው የጠቆሙት፡፡

አምባሳደሩ ፥ ምንም እንኳን በኢትዮጵያ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ራስን በምግብ ለመቻል ጥረት እየተደረገ ቢሆንም በአንዳንድ የኢትዮጵያ ክፍሎች ድርቅ በመከሰቱ ምክንያት ግን የሰብዓዊ ድጋፍ ማስፈለጉን ነው አጽንኦት ሠጥተው የተናገሩት።

የፓርላማ አባላቱ ፥ በኢትዮጵያ እየተስተዋለ ያለውን ፖለቲካዊ መሻሻል እና ሀገሪቷ የያዘችውን በምግብ እህል ራስን የመቻል መርሃ-ግብር ማድነቃቸው በመረጃው ተመላክቷል፡፡

የፓርላማ አባላቱ ኢትዮጵያን መደገፋቸውን እንደሚቀጥሉ እና የእንግሊዝ ባለሐብቶችም በኢትዮጵያ መዋዕለ-ንዋያቸውን እንዲያፈሱ መረጃ እንደሚሰጡም ነው የጠቆሙት፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version