አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚስጥራዊ መለያ እና የክፍያ መፈጸሚያ ሥርአት አገልግሎት ሰጪ ከሆነው ከጃፓኑ ቶፓን ጋር የመግባቢያ ሠነድ ተፈራርመዋል፡፡
ኩባንያው በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚስጥራዊ መለያ እና የክፍያ መፈጸሚያ ሥርአት አገልግሎት ሰጪ ከሆኑ ድርጅቶች መካከል በቀዳሚነት የሚጠቀስ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ማሞ ምህረቱ አስታውቀዋል፡፡
ከኩባንያው ጋርም በቀጣይ ኢትዮጵያን የደኅንነት እና የሚስጥራዊ ህትመት ኢንዱስትሪ የመግባቢያ ስምምነት መፈረሙንም ጠቁመዋል።
ቶፓን በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ14 ቢሊየን ዶላር በላይ በሆነ የገቢ መጠን የሚንቀሳቀስ እና በ20 ሀገራት የሚሠራ ኩባንያ ነው።
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

