አዲስ አበባ፣ መጋቢት 2፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ጋር በስልክ ተወያዩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዋና ፀሃፊው ጋር በቀጠናዊ የሰላም ሁኔታ እና የደህንነት ስራዎች ዙሪያ መምከራቸውን በተመድ የኢትዮጵያ ቋሚ ተጠሪ የትዊተር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
አንቶኒዮ ጉተሬዝ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ለውጥ እንዲሁም አካባቢያዊ ልማት ድርጅታቸው እንደሚደግፍ ገልፀዋል።
ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://t.me/fanatelevision

