Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኤርባስ አውሮፕላን አምራች ኩባንያ ጋር የኤርባስ A350-1000 ትዕዛዝ ተፈራረመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሚያደርገውን የኤርባስ A350-1000 ትዕዛዝ ከኤርባስ አውሮፕላን አምራች ኩባንያ ጋር ተፈራርሟል።

አየር መንገዱ ከዚህ በፊት 22 ኤርባስ A350-900 አውሮፕላን በማዘዝ 16ቱን ተረክቦ ስራ ላይ ማዋሉን አስታውቋል፡፡

ከተቀሩት የኤርባስ A350-900 አውሮፕላን ትዕዛዞች አራቱ ወደ ኤርባስ A350-1000 እንዲቀየሩ ከኤርባስ አውሮፕላን አምራች ኩባንያ ጋር  ስምምነት መደረጉን ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በዚህ ስምምነት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርባስ A350-1000ን አገልግሎት ላይ ያዋለ የመጀመሪያው የአፍሪካ አየር መንገድ እንደሚያደርገው ተጠቁሟል፡፡

Exit mobile version