Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በታንዛንያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 60 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በታንዛንያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 60 ኢትዮጵያውያን በፈቃዳቸው በዛሬው ዕለት ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

በታንዛንያ የዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት ፕሮግራም ሃላፊ ዴቪድ ሆፍሜየር በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ ዜጎቹ በዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት፣ በታንዛንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲና የታንዛንያ የስደተኞች ጉዳይ ጽሕፈት ቤት ባደረጉት ትብብር ነው ወደ ሀገራቸው የተመለሱት፡፡

ሃላፊው ኢትዮጵያውያኑ በአራተኛ ዙር ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ የስዊድን መንግሥት ላደረገው የገንዘብ ድጋፍ እና ድርጅቶቹ ላደረጉት ትብብት ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ዜጎች በቀጣይ በተቀመጠላቸው የጉዞ መርሐ ግብር መሠረት ወደ ኢትዮጵያ መመለስ እንዲችሉ አስፈላጊ የሆኑ ቅድመ ሁኔታዎች በመሟላት ላይ እንደሚገኙም ተጠቁሟል፡፡

Exit mobile version