Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

1 ሺህ 33 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 1 ሺህ 33 ኢትዮጵያውያን በዛሬው ዕለት ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡

ከተመላሾቹ ውስጥ 1 ሺህ 24 ወንዶች፣ 2 ሴቶች ፣ 7 ህፃናት እና እድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች እንደሚገኙበት ተገልጿል፡፡

ለተመላሽ ዜጎች ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ወደተዘጋጀላቸው የማቆያ ማዕከላት እንዲሄዱ መደረጉንም ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version