Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኤጀንሲው ከመስከረም ጀምሮ የቀለም ማኅተም በደረቅ ማኅተም እንደሚቀይር አስታወቀ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 21 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ከመጪው መስከረም ወር ጀምሮ የጽህፈት ቤቶቹን የቀለም ማኅተሞች በደረቅ ማኅተሞች እንደሚቀይር አስታወቀ፡፡

የአዲስ አበባ ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ታከለ ነጫ ÷ ማኅተሞቹ የሚቀየሩት በከተማዋ የሚስተዋለውን የሰነድ ማጭበርበር ለማስቀረት ነው ብለዋል፡፡

ይህን ተግባራዊ ለማድረግም ኤጀንሲው የብረት ማኅተሞች ከውጭ ማስገባቱን ተናግረዋል፡፡

የአማራና ኦሮሚያ ክልል ወሳኝ ኩነት ምዝገባ አገልግሎት ተቋም አመራሮችና ባለሙያዎች በኤጀንሲው ተገኝተው የልምድ ልውውጥ ማድረጋቸውንም ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version