Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ነገ ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት በመዲናዋ ይሰጣል

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ነገ ጳጉሜን 4 ነጻ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት በመዲናዋ እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ አስታወቁ።

ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ፥ “የአገልጋይነት ቀን” ን ምክንያት በማድረግ ነው የነጻ ትራንስፖርት አገልግሎት እንደሚሰጥ የገለጹት፡፡

በዚህም አዳዲስ የሚሰማሩ አውቶቡሶችን ጨምሮ ፣ ሸገር የብዙኃን ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅትና አንበሳ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት ድረስ በነፃ አገልግሎት እንደሚሰጡ ገልጸዋል፡፡

አክለውም ፥ ጷጉሜን 4 “የአገልጋይነት ቀን” ብለን የሰየምነው ሁሉም ዜጋ የአገልጋይነት ባሕልን በማዳበር ሁለንተናዊ ለውጥ ማምጣት እንድንችል ነው ብለዋል፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ መጪው ዘመን የደስታ፣ የፍስሃ እና የስኬት እንዲሆን ተመኝተዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version