Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በጎንደር ከተማ ለጥምር ጦሩ 17 ሚሊየን ብር የሚገመት ድጋፍ ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር ከተማ አስተዳደር ለጥምር ጦሩ ድጋፍ በዓይነትና በጉልበት 17 ሚሊየን ብር የሚገመት ድጋፍ መሰብሰቡ ተገለጸ፡፡

የጎንደር ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ባዮ አቡሃይ በድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብሩ ላይ እንዳሉት÷ አሸባሪው ህወሓት የከፈተውን ጦርነት ለመመከት የከተማው ህዝብ ለጥምር ጦሩ 17 ሚሊየን ብር የሚገመት የዓይነትና የጉልበት ድጋፍ አድርጓል፡፡

በአድርቃይ እና በወፍ አርግፍ ግንባር እንዲሁም በጎንደር ከተማ 2 ሆስፒታሎች ለሚገኙ ቁስለኞች ድጋፉ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል ።

የከተማው ህዝብ በስንቅ ዝግጅት እያደረገ ያለው ድጋፍ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የጠቆሙት ምክትል ከንቲባው፥ ከስንቅ ዝግጅት ጎን ለጎን የከተማው ህዝብ ተደራጅቶ አካባቢውን ከሰርጎ ገቦች ሊጠብቅ ይገባል ብለዋል ።

የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እና የህብረተሰቡ የደጀንነት ተግባርም አሸባሪው ህወሓት እስከሚደመሰስ ድረስ ሊቀጥል ይገባልም ነው ያሉት ፡፡

በአበራ መኮንን

Exit mobile version