Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

መንግስት ለዓለምአቀፍ ባለሐብቶች ከፍተኛ ጥበቃ እንደሚያደርግ ገለጸ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) መንግስት ለዓለም አቀፍ ባለሐብቶች በማንኛውም ጊዜ የኢንቨስትመንት ጥበቃ ለማድረግ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ለሚገኙ ዓለም አቀፍ ባለሐብቶች ማኅበር አባላት በሀገራችን ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

በውይይታቸው ወቅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ተሥፋዬ ይልማ እና የኮሚሽኑ አመራሮች ከማኅበር አባላቱ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

በኢትዮጵያ በተለያዩ መስኮች መሰማራት ለሚፈልጉ ባለሐብቶች ያለምንም የፀጥታ ሥጋት ኢንቨስትመንታቸው እንዲሳለጥ ከጎናቸው እንደሚቆሙ ማረጋገጣቸውን ከኢንቨስትመንት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version