Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የሲዳማ ክልል ለጀግናው መከላከያ ሠራዊት የ26 ሚሊየን ብር የገንዘብና የዓይነት ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 20 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትና ህዝብ ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት የ26 ሚሊየን ብር የገንዘብና የዓይነት ድጋፍ አደረገ።

ድጋፉን የተረከቡት የመከላከያ ሚኒስትር ዴኤታ ማርታ ሉዊጂ ÷ የኢትዮጵያን ሉዓላዊ አንድነት ለማስቀጠል በቁርጠኝነት እየታገለ ለሚገኘው ጀግናው ሰራዊታችን ላበረከታችሁት አስተዋጽኦ ክብር አለን ብለዋል።

የሲዳማ ክልል የብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ኤልያስ ÷ ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ደጀንነታችንን ለማሳየት 20 ሚሊየን የገንዘብና 6 ሚሊየን የሚገመት የዓይነት ድጋፍ አድርገናል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version