አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጣና ፎረም ላይ ለመሳተፍ ኢትዮጵያ የሚገኙት የሶማሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዛ አብዲ በቅርቡ የተመረቀውን የሣይንስ ሙዚየም ጎበኙ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዛ የፓንአፍሪካን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ 2022 ዐውደ ርዕይን እና በሣይንስ ሙዚየም ለዕይታ የቀረቡ የሣይንስ እና ቴክኖሎጂ ውጤቶችን መጎብኘታቸውን የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት መረጃ ያመላክታል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዛ አብዲ በጉብኝቱ ወቅት ኤግዚቢሽኑ የአፍሪካን ወንድማማችነት የሚወክል መሆኑን ገልጸዋል፡፡
መሰል መድረኮች አፍሪካን በሣይንስና በቴክኖሎጂ የላቀች አህጉር ለማድረግ ከፍተኛ ሚና እንዳቸውም ጠቁመዋል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!