አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 6 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በጽህፈት ቤታቸው አማካኝነት በጎንደር ከተማ እየተገነባ ያለውን የዳቦ ፋብሪካ የግንባታ ሂደት ጎበኙ።
ፋብሪካው በዋናነት በዝቅተኛ ገቢ የሚተዳደሩ የከተማዋን ነዋሪዎች ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው።
የፋብሪካው ግንባታ ከተጀመረ 7 ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን÷ በጥር ወር 2015 ዓ.ም ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ፋብሪካው ሙሉ ለሙሉ ወደ ስራ ሲገባ በቀን እስከ 200 ሺህ ዳቦ የማምረት አቅም እንደሚኖረው መገለፁን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!