አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሥራና ክኅሎት ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል በኢትዮጵያ ከጣሊያን አምባሳደር አጎስቲኖ ፓሌሴ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም በኢትዮጵያ እና ጣሊያን መካከል በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና በትብብር መሥራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን በኢትዮጵያ የጣሊያን ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡
በተጨማሪም የእውቀት ሽግግር ማድረግ ስለሚቻልበት ሁኔታ፣ የልማት ማዕከላትን ስለመገንባት እንዲሁም በሌሎች የትብብር መስኮች ላይ መወያየታቸው ተገልጿል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!