Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በዋግኽምራ ዞን ለ42 ሺህ ወገኖች ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዋግኽምራ ዞን ለሚገኙ 42 ሺህ ወገኖች የሚውል ምግብና ምግብ ነክ ያልሆነ ድጋፍ ማድረጉን የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ አስታወቀ፡፡
በዞኑ ዝቋላ ወረዳ፣ ፅፅቃ ከተማ እና አካባቢው ለሚገኙ እና ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው 30 ሺህ ወገኖች የምግብ ድጋፍ መደረጉን የዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ልዑክ በኢትዮጵያ መረጃ ያመላክታል፡፡
እንዲሁም ለ12 ሺህ ሰዎች ደግሞ ምግብ ነክ ያልሆነ የቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉ ነው የተገለጸው፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version