Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 200 የውሃ መሳቢያ ፓምፖች ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር 200 የውሃ መሳቢያ ፓምፖችን ለአዲስ አበባ ከተማ ድጋፍ አድርጓል፡፡

የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንደገለጹት÷ የድጋፉ ዓላማ በከተማዋ የተጀመረው የከተማ ግብርና እያሳየ ያለው መነቃቃት በበጋው ወቅትም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ነው፡፡

በድጋፍ መልክ የተበረከቱት ፓምፖችም÷ በመዲናዋ በክረምት የተጀመረው የከተማ ግብርና ቀጣይነት እንዲኖረው ውሃ ባለበት አካባቢ ሁሉ መሳብ የሚችሉ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ድጋፉን የተረከቡት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው÷ ለከተማዋ አቅም ከሆኑ ተቋማት መካከል የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር አንዱ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በድጋፍ መልክ የተበረከቱት የውሀ መሳቢያ ፓምፖችም÷ በከተማዋ እየተሠራ ያለው ግብርና የተፈለገውን ውጤት እንዲያመጣ ያግዛሉ ብለዋል።

እነደዚህ ያለው ትብብር የምግብ ዋስትናን ለማረጋጥ እንደሚረዳ ጠቁመው÷ የውሃ መሳቢያ ፓምፖቹን ለሚመለከተው አካል እንደሚያስረክቡም ተናግረዋል።

በቅድስት ብርሃኑ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version