Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኤደን ሀዛርድ ከቤልጂየም ብሔራዊ ቡድን ራሱን አገለለ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አሁን በሪያል ማድሪድ እየተጫወተ የሚገኘው ኤደን ሀዛርድ ከቤልጂየም ብሔራዊ ቡድን ራሱን ማግለሉን ይፋ አድርጓል፡፡

ቤልጂየም በጊዜ ከዓለም ዋንጫው መሰናበቷን ተከትሎ ነው ኤደን ሀዛርድ ከብሔራዊ ቡድኑ ራሱን ያገለለው፡፡

የ31 ዓመቱ ሀዛርድ ለሀገሩ በ126 ጨዋታዎች ተሰልፎ 33 ጎሎችን ማስቆጠሩን ጎል ዶት ኮም ዘግቧል፡፡

የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ቀደም ሲል ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸው ይታወሳል፡፡

Exit mobile version