Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ በጤና ሳይንስ ያሰለጠናቸውን 811 ተማሪዎች አስመረቀ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ወለጋ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው እለት በጤና ሳይንስ ያሰለጠናቸውን 811 ተማሪዎች አስመርቋል፡፡

ከተመራቂዎች መካከል 351 ተማሪዎች በመጀመሪያ ዲግሪ 457ቱ ደግሞ በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ናቸው ተብሏል፡፡

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ሀሰን ዩሱፍ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ተመራቂዎች በሰለጠኑበት ሙያ ህዝቡን በተነሳሽነትና በቅንነት እንዲያገለግሉም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

 

Exit mobile version