Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በሰላም ስምምነቱ አተገባባር ዙሪያ ለወታደራዊ አታሼዎች ማብራሪያ እየተሰጠ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሰላም ስምምነቱ አተገባባር ዙሪያ ለወታደራዊ አታሼዎች ማብራሪያ እየተሰጠ ነው፡፡

በመድረኩ በፌዴራል መንግስትና በህወሓት መካከል የተፈረመውን የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት አተገባበር በተመለከተ ነው ማብራሪያ እየተሰጠ የሚገኘው።

የመከላከያ የውጭ ግንኙነት ወታደራዊ ትብብር ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ የሰላም ስምምነቱ አተገባበር ያለበትን ደረጃና አጠቃላይ ሂደት አብራርተዋል።

በዚሁ ማብራሪያ የሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች ተሳትፈዋል።

የወታደራዊ አታሼዎቹ መንግሰት ለሰላም ስምምነቱ መከበር ያለውን ቁርጠኝነት በተለያዩ ተግባሮቹ አሳይቷል፤ይህም ትርጉም ያለውና የሚደነቅ መሆኑን ገልፀዋል።

በሐብታሙ ተክለስላሴ

Exit mobile version