Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

50 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሕንድ በተዘጋጀው ሥልጠና ላይ እየተሳተፉ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 50 የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሕንድ በተዘጋጀው የአራት ቀናት የሥልጠና መርሐ-ግብር ላይ እየተሳተፉ ነው፡፡

ልዑካን ቡድኑ የኢፌዴሪ መንግስት ዋና ተጠሪዎችን ጨምሮ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች፣ምክትል ሰብሳቢዎች፣ የክልል ፓርላማ ፕሬዚዳንቶች በአጠቃላይ 50 የኢፌዴሪ ፓርላማ አባላትን ያቀፈ ነው ተብሏል፡፡

መርሐ ግብሩ በሕንዱ የዴሞክራሲዊ ፓርላማ ጥናት እና ሥልጠና ኢኒስቲትዩት የተዘጋጀው መሆኑን በኢትዮጵያ የሕንድ ኤምባሲ መረጃ አመላክቷል፡፡

ልዑካኑ ሕንድ ኒው ዴልሂ ሲደርሱ በሀገሪቱ የኢትጵያ አምባሳደር እና የሕንድ ማኅበረሰብ አባላት አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version