Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በስራ ዕድል ፈጠራ ፕሮጀክት ላይ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ውይይት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በስራ ዕድል ፈጠራ ፕሮጀክት ላይ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር እየመከረ ነው፡፡

በመድረኩ የኢትዮጵያ፣ የኬንያ እና የታንዛኒያ ተወካዮች እንዲሁም የዓለም ባንክ፣ የምስራቅ አፍሪካ የክህሎት ትራንስፎርሜሽን እና ቀጠናዊ ትስስር ፕሮጀክት አመራሮች ተገኝተዋል።

ወይይቱ በሃይል አቅርቦት፣ በማኑፋክቸሪንግ እና በትራንስፖርት የስራ ዕድል ፈጠራ ያተኮረ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ ከሚተገብርባቸው የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የተሻለ አፈፃፀም አስመዝግባለች።

በፕሮጀክቱ ከሚደገፉ የልህቀት ማዕከላት የስልጠና መሠረተ ልማት ዝርጋታ ባሻገር ፕሮጀክቱ በክህሎት ልማትና ነፃ የጉልበት ዝውውር በማስፈን በቀጠናው ያሉ ሀገራትን ከማስተሳሰር አንፃር ሚናው ከፍተኛ ነው ማለታቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version