Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በቦስተን ማራቶን አትሌት አማኔ በሪሶ 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቀች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሜሪካ ቦስተን ማራቶን አትሌት አማኔ በሪሶ 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቃለች፡፡

አማኔ ርቀቱን 2 ሰዓት ከ21 ደቂቃ 50 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ነው ሁለተኛ ደረጃን መያዝ የቻለችው፡፡

ርቀቱን ኬንያዊቷ አትሌት ሄለን ኦብሪ 2 ሰዓት ከ21 ደቂቃ 38 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመግባት በበላይነት አጠናቅቃለች፡፡

በወንዶች የቦስተን ማራቶን ኬንያዊው ኢቫን ቼቤት ቀዳሚ ሲሆን÷ ታንዛኒያዊው አትሌት ጋብሬል ጌይ 2ኛ እንዲሁም ቤንሱን ኪፕሪቶ ከኬንያ 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቀዋል፡፡

ኢትዮጵያን በመወከል በርቀቱ የተሳተፈው ሹራ ቂጣታ 14ኛ ደረጃን በመያዝ ማጠናቀቁን ከቦስተን ማራቶን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version