Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ከሚያዝያ 16 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ የነዳጅ ግብይትን ከኤሌክትሮኒክስ ሥርዓት ውጪ መፈጸም አይቻልም – ቢሮው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከሚያዝያ 16 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ የነዳጅ ግብይትን ከኤሌክትሮኒክስ ሥርዓት ውጪ በሚፈፅሙ የነዳጅ ማደያዎች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ገለጸ፡፡

ከሚያዚያ 16 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅነት በኤሌክትሮኒክስ ሥርዓት ብቻ ተግባራዊ እንደሚደረግ ቢሮው አስታውቋል፡፡

ስለሆነም በአዲስ አበባ የሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች በሙሉ ከሚያዝያ 16 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ የነዳጅ ተጠቃሚዎችን በኤሌክትሮኒክስ ሥርዓት ብቻ ለማስተናገድ የቅድመዝግጅት ስራቸውን ከወዲሁ እንዲያጠናቅቁ ቢሮው አሳስቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version