Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ በኦሮሚያ ክልል በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች 33 ሚሊየን ብር የሚገመት የዓይነት ድጋፍ አደረገ፡፡

ድጋፉ ከትምህርት ማህበረሰቡ የተሰበሰበ መሆኑን የቢሮው ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

አልባሳትን ጨምሮ ምግብ እና የእንስሳት መኖን ያካተተ ድጋፍ ስለመሆኑም ጠቁመዋል፡፡

የኦሮሚያ ክልል ቡሳ ጎኖፋ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ኤልዳና ሱሌማን በድርቅ የተጎዱ ወገኖችን መልሶ የማቋቋም ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version