Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ከሠሃራ በታች ባሉ ሀገራት የጀርመን ጉዳይ አሥፈፃሚ በሱዳን ለተከሰተው ግጭት መፍትሄ ለመሻት ከኢጋድ ዋና ጸሐፊ ጋር መከሩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)ከሠሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት እና በሳኅል ቀጠና የጀርመን የውጭ ጉዳይ አሥፈጻሚ ዳይሬክተር ክርስቶፍ ሬዝላፍ በሱዳን ለተከሰተው ግጭት መፍትሄ ለመሻት ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግስታት (ኢጋድ) ዋና ጸሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ.ር) ጋር መክረዋል፡፡

ክርስቶፍ ሬዝላፍ ÷ በጉዳዩ ላይ ከኢጋድ በተጨማሪ ከኢትዮጵያ መንግስት እንዲሁም ከአፍሪካ ኅብረት ባለሥልጣናት ጋር እንደሚመክሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡

በሱዳን የተቀሰቀሰው ጦርነት በአስቸኳይ መቆም እንዳለበትና ሁለቱን ወገኖች ለማስማማት ፖለቲካዊ መፍትሄ እንደሚያሻም አሳስበዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version