አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለ82ኛው የኢትዮጵያ ዐርበኞች ድል መታሰቢያ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ከንቲባዋ በመልዕክታቸው÷የአሁኑ ትውልድ ነጻነቷ የተከበረ ሉዓላዊት ኢትዮጵያ ባለቤት እንዲሆን አባት እና እናት አርበኞች ታላቅ ተጋድሎ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
ይህ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ሲዘከር የሚኖር ታልቅ ድል ነው ያሉት ክንቲባዋ÷ ቀጣዩ ትውልድም የአባቶቹን ፈለግ በመከተል የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

