Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

አቶ ሙስጠፌ መሃመድ ከጀረር ዞን ነዋሪዎች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሃመድ ከጀረር ዞን ነዋሪዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይት መድረኩ በሕዝቡ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች፣ በምርትና ምርታማነት ማሳደግ፣ በሰላምና ጸጥታ እንዲሁም በልዩ ኃይል መልሶ ማደራጀት ዙሪያ ምክክር ተደርጓል፡፡

አቶ ሙስጠፌ÷ ሰሞኑን በሁሉም የክልሉ አከባቢዎች በተለይ በወንዞችና ተፋሰስ አከባቢ በጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው የጎርፍ አደጋ ለተጎዱ ዜጎች እየተደረገ ያለውን ድጋፍ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ተጎጂዎችን መልሶ ለማቋቋም የክልሉ መንግሥት ከሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ ከአየር ኃይልና ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር ድጋፍ እያደረገ መሆኑንም አስረድተዋል።

በርዕሰ መስተዳደሩ የተመራ ከፍተኛ የክልሉ ባለስልጣናት በቀጣይም ከሌሎች የሕበረተሰብ ክፍሎች ጋር እንደሚወያይ የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
Exit mobile version