Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የአዲስ አበባና ሸገር ከተማ አስተዳደሮች በደኅንነት ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ እና የኦሮሚያ ሸገር ከተማ አስተዳደሮች በሠላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የስምምነት ሠነድ ተፈራረሙ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ቡዜና አልቃድር ፣ የሸገር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) ፣ የአዲስ አበባ ከተማ የሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ፣ በየደረጃው የሚገኙ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የሃይማኖት አባቶች እና አባገዳዎች በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተዋል፡፡

በመድረክ ሁለቱን ከተሞች በጋራ መሥራት የሚያስችላቸው ሠነድ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ቡዜና አልቃድር፥ የሕዝብን ሠላምና ደኅንነትን ለማስጠበቅ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ኢኖሚያዊና አስተዳደራዊ ጉዳዮችን በኃላፊነትና በተጠያቂነት መሥራት ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ የሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ በበኩላቸው ÷ “ከአጎራባች የሸገር ከተማ አስተዳደር ጋር በምናከናውነው ጠንካራ ሠላም እና ፀጥታን የማስጠበቅ ሥራዎች ኅብረተሰቡን እያሳተፍን ነው” ብለዋል።

የሸገር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) ÷ ወንጀል ፈፃሚዎችን በጋራ በመከላከል የሕዝቡን አንድነት በማጠናከር የመረጃ ልውውጦችን በቅንጅት በመሥራት ላይ እንገኛለን ማለታቸውን የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
Exit mobile version