Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ የዱባይ ዓለም አቀፍ ምክር ቤት የመካከለኛው ምስራቅና የአፍሪካ ኃላፊ ጋር ተወያዩ

 

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢንቨስትመንት ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ የዱባይ ዓለም አቀፍ ምክር ቤት የመካከለኛው ምስራቅና የአፍሪካ ኃላፊ ከሆኑት ካሊድ አል አሊ ጋር በዱባይ ተወያይተዋል፡፡

በውይይቱ ÷ ከቀጠናው አዲስ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ ስለሚቻልባቸው ስትራቴጂካዊ መንገዶችና የኢንቨስትመንት አጋርነቶች እንዲሁም የጋራ ፕሮሞሽን ስራዎች ዙሪያ መምከራቸውን ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version