Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ አውደ-ርዕይ ላይ የሚደረግ ተሳትፎን ማሳደግ ያስፈልጋል- በለጠ ሞላ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ አውደ-ርዕይ ላይ የሚደረግ ተሳትፎን ማጠናከርና ማሳደግ ያስፈልጋል ሲሉ የኤኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር  በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡

በሞሮኮ በሚካሄደው ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ አውደ-ርዕይ ላይ የሚሳተፉ ስምንት የኢትዮጵያ ስታርትአፖችና አይሲቲ ቢዝነሶች ሽኝት ተደረገላቸው።

ስታርት አፕ ድርጅቶቹ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ባወጣው ውድድር  የተመረጡ ሲሆኑ÷ በጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ ድጋፍ እና ስፖንሰር ተደርገዋል።

እነዚህ ስታርትአፖች እና የአይሲቲ ቢዝነሶች ኢትዮጵያን በመወከል በዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ አውደ-ርዕይ ላይ የሚሳተፉ ሲሆን÷ በኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሽኝት ተደርጎላቸዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኤኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር)÷ የኢትዮጵያን ተሞክሮ በአለምአቀፉ የቴክኖሎጂ አወደ ርዕይ ለማሳየት የተፈጠረው እድል  መልካም የሚባል ጅምር  ነው ብለዋል፡፡

በቀጣይም እንዲህ ያሉ ተሳትፎችን በይበልጥ ማጠናከርና ማስፋት ያስፈልጋል ማለታቸውን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version