Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በሞሮኮ እየተዘጋጀ ባለዉ የጂአይቴክስ አፍሪካ ኢትዮጵያን ወክለዉ የተገኙ ጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎችን ተጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር በሞሮኮ እየተጋጀ ባለዉ የጂአይቴክስ አፍሪካ ኢትዮጵያን ወክለዉ የተገኙ ጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎችን ጎበኙ፡፡

በሞሮኮ ማረከሽ በአፍሪካ ለመጀምሪያ ጊዜ በተካሄደዉ ኮንፈረንስ ላይ ‘‘የአቅም ግንባታ ስራ ለሙያዊ ልህቀትና ኢኮኖሚ ልማት’’ በሚል መድረክ ላይ የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር ሰለሞን ሶካ ተካፍለዋል፡፡

ከመድረኩ ጎን ለጎን ጀማሪ ኢትዮጵያውያን ስራ ፈጣሪዎችን ጎብኝተዋል።

ኮንፈረንሱ ትኩረቱን በሳይበር ደህንነት፣ በክላዉድ ኮምፒዉቲንግ ፣ በአርተፍሻል ኢንተለጀንስ፣ በፊንቴክ ፣ በዲጂታል ከተማ፣ አግሪ ቴክ መሰል የቴክኖሎጂ ዘርፎች አድርጓል ነው የተባለው፡፡

በዚህ መርሐ ግብር ላይም ኢትዮጵያ ምርትና አገልግሎቶቿን እያስተዋወቀች እንደምትገኝ ተጠቁሟል፡፡

በጉብኝቱ ወቅት በሳይበርና መሰል ጉዳዮች ላይ አቅም ያላቸዉ አካላት ኢመደአ በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባና ተቋሙ በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ አንስተዋል።

በጉብኝቱ የኢመደአ ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ተሳትፈዋል።

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version