Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከ ዩኒዶ ተወካይ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዲሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በዛሬው ዕለት ከተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት(ዩኒዶ) ተወካይ ኦሬሊያ ካላብሮን ጋር ተወያይተዋል፡፡

ምክር ያደረጉት ፥ በኢትዮጵያ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት (ዩኒዶ) መካከል ያለውን አጋርነት ለማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ነው።

አምባሳደር ምስጋኑ በዚህ ወቅት ፥ ኢትዮጵያ ከዩኒዶ ጋር በአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪዎች፣ በጨርቃ ጨርቅ፣ በቆዳና ቆዳ ውጤቶችና በፋርማሲዩቲካል ምርቶች ላይ አጋርነቷን ለማሳደግ ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።

ተወካይ ኃላፊዋ ኦሬሊያ ካላብሮን በበኩላቸው÷ የኢትዮጵያ መንግስት እየወሰደ ያለውን የማሻሻያ እርምጃዎች አድንቀዋል፡፡

በተጨማሪም ፥ የተባበሩት መንግስታት ድርጅተ ኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት በኢትዮጵያ ለማከናወን ስላቀዳቸው ተግባራት ማብራራታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version