Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የተባበሩት መንግሥታት ሥነ ሕዝብ ፈንድ በአፋር ክልል የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚያሳድግ ገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ከተባበሩት መንግሥታት ሥነ ሕዝብ ፈንድ (ዩ ኤን ኤፍ ፒ ኤ) የኢትዮጵያ ዋና ተጠሪ ካፊ ኩዋሜ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም ዩ ኤን ኤፍ ፒ ኤ ለአፋር ክልል የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል በሚችልበት አግባብ ላይ መክረዋል፡፡

ተቋሙ የክልሉ የስነ ተዋልዶ እና የእናቶችን ጤና ለማሻሻል እንዲሁም ለአቅመ ደካማ ሴቶች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠሉ ተመላክቷል፡፡

ካፊ ኩዋሜ ÷የተባበሩት መንግሥታት ሥነ ሕዝብ ፈንድ ለአፋር ክልል የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚያሳድግ ቃል ገብተዋል።

ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በበኩላቸው÷ ተቋሙ እስካሁን ለአፋር ክልል ላደረገው ዘርፈ ብዙ ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

 

 

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version