አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢድ-አል አድሃ (አረፋ) በዓልን ምክንያት በማድረግ ነገ ማለዳ 9 ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ የመከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
ነገ ሰኔ 21 ቀን 2015 ዓ.ም የሚከበረውን የኢድ-አል አድሃ (አረፋ) በዓልን ምክንያት በማድረግ ማለዳ 12 ሰዓት ላይ 9 ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ በመከላከያ ሚኒስቴር ስነ-ልቦና ግንባታ ዳይሬክቶሬት ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ገልጿል፡፡