Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

አቶ ጌታቸው ረዳ ሙስሊሙ ሕብረተሰብ የመተጋገዝ ባህሉን ይበልጥ እንዲያጠናክር አስገነዘቡ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ ሙስሊሙ ሕብረተሰብ ያለውን የመተጋገዝ ባህል ይበልጥ እንዲያጠናከር ጠይቀዋል፡፡

1ሺህ 444ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በመቀሌ ከተማ መከበሩን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

አቶ ጌታቸው ረዳ በበዓሉ አከባበር ላይ ባስተላለፉት መልዕክት÷ በአካባቢያችን ያሉት ተፈናቃይ ወገኖችን ለማገዝ እያደረጋችሁ ያለው በጎ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል፡፡

የትግራይ ክልል ከፍተኛ ምክርት ቤት ኃላፊ ሓጂ አደም አብዱልቃድር በበኩላቸው÷ በተፈጠረው ሰላም በዓሉን ተረጋግተን ማክበር ችለናል ነው ያሉት፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version