Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የ2015 የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል የ2015 የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በምሥራቅ ሸዋ ዞን ተካሄደ።

ከክልል እስከ ወረዳ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች እና ከክልሉ የተወጣጡ ግንባር ቀደም ወጣቶች በመርሐ- ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ተሳትፈዋል፡፡

በዕለቱም የችግኝ ተካለ፣ የቤት ዕድሳት እና የደም ልገሳ መከናወኑን የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

በኦሮሚያ ክልል በ2015 የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት 9 ነጥብ 5 ሚሊየን ወጣቶች እንደሚሳተፉ ተገልጿል፡፡

በዚህም ከ23 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ነው የታሰበው፡፡

በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱም 3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገመት አገልግሎትእንደሚሰጥ ነው የተመላከተው፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version