አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል የ2015 የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በምሥራቅ ሸዋ ዞን ተካሄደ።
ከክልል እስከ ወረዳ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች እና ከክልሉ የተወጣጡ ግንባር ቀደም ወጣቶች በመርሐ- ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ተሳትፈዋል፡፡
በዕለቱም የችግኝ ተካለ፣ የቤት ዕድሳት እና የደም ልገሳ መከናወኑን የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡
በኦሮሚያ ክልል በ2015 የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት 9 ነጥብ 5 ሚሊየን ወጣቶች እንደሚሳተፉ ተገልጿል፡፡
በዚህም ከ23 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ነው የታሰበው፡፡
በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱም 3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገመት አገልግሎትእንደሚሰጥ ነው የተመላከተው፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!