Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በቢሾፍቱ ከተማ በ2 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ተመረቁ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቢሾፍቱ ከተማ በ2 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነቡ 85 ፕሮጀክቶች ተመረቁ፡፡

በዛሬው ዕለት ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከል÷ ደረጃውን የጠበቀ የአስፋልት መንገድ፣ የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣  እንዲሁም የገበያ ማዕከል እና የሕዝብ ቤተ መጻሕፍትን ጨምሮ ሌሎችም እንደሚገኙበት የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመላክታል፡፡

በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ፈቃዱ ተሰማ በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር÷ የማንጨርሳቸውን ፕሮጀክቶች አንጀምርም፤ የጀመርነውን ደግሞ በጥራት ጨርሰን ለሕዝብ ተጠቃሚነት እናውላለን ብለዋል፡፡

በተመሳሰይ በኦሮሚያ ክልል በቦረና እና ባሌ ዞኖች እንዲሁም በነቀምት እና አሰላ ከተሞች የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለሕዝብ አገልግሎት ክፍት ሆነዋል፡፡

Exit mobile version