Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር) ከአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) እና የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ ማህማት በሱዳን ወቅታዊ ጉዳይ ላይ መክረዋል።

ሁለቱ ተቋማት በሱዳን ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ያላቸው ቁርጠኝነት የማይናወጥ መሆኑን ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

ኢጋድ እና የአፍሪካ ህብረት በሱዳን ዘላቂ የሆነ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረስ፣ ጦርነቱ እንዲቆም እና ሀገሪቱን ወደ ፖለቲካው መስመር ለመመለስ በጋራ ጥረት እያደረጉ መሆኑንም አንስተዋል፡፡

Exit mobile version