Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ፍትሃዊና ውድድርን ማዕከል ያደረገ የንግድ ትስስር ለመፍጠር እየተሰራ ነው ተባለ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) እንደሀገር ፍትሃዊና ውድድርን ማዕከል ያደረገ የንግድ ትስስር ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ገብረመስቀል ጫላ ፥ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተከናወነው የወጪ ንግድ 3 ነጥብ 64 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱን ተናግረዋል፡፡

ከተገኘው ገቢ ውስጥ 79 በመቶ የሚሆነው ድርሻ የግብርናው ዘርፍ መሆኑን ነው ሚኒስትሩ ያብራሩት፡፡

አፈጻጸሙ ከአምናው አንጻር ሲታይ የ487 ሚሊየን ዶላር ቅናሽ ማሳየቱን ጠቁመው፥ለዚህ ምክንያቱ የዓለም ገበያ መቀዛቀዝ፣ የኮንትሮባንድ ንግድና ምርቶችን በወቅቱ ያለማቅረብ ችግሮች መሆናቸውን አስረድተዋል።

በዘርፉ እየተስተዋለ ያለውን የአሰራር ክፍተት በፖሊሲ ደረጃ በማየት ማስተካከል እንዲቻል የተለያዩ አዋጆችና ደንቦች መዘጋጀታቸውንም ነው የተናገሩት።

የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት የተጀመረው የሰንበት ገበያ ሥርዓት እና በሁሉም አካባቢ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የሚከናወነው ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ማንሳታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version