Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን መቀበል ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሁሉንም የመደበኛና የድህረ ምረቃ ተማሪዎች ከዛሬ ሐምሌ 29 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እየተቀበለ እንደሚገኝ አስታወቀ።

በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ተከስቶ በነበረው ግጭት ምክንያት ለሁለት ዓመት የመማር ማስተማር ስራውን ኣቋርጦ የነበረው ዩኒቨርሲቲው፤ መሰረታዊ ጥገናዎችን በማድረግ ተማሪዎችን መቀበል መጀመሩን ገልጿል።

በሚቀጥለው ማክሰኞ የዩኒቨርሲቲው ቦርድ ኣባላት፣ የዩኒቨርሲቲው ማሕበረሰብ አባላት እንዲሁም ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት ይፋዊ የአቀባበል ስነ-ስርዓት እንደሚካሄድ ከዩኒቨርሲቲው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

Exit mobile version